መላእክት:አበው:ነቢያት:ሐዋርያት:ሰማዕታት:ጻድቃን:በቤተክርስቲያን ቀኖና ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ።
ዘሌ 9:2:1ጴጥ1:15:ዮሐ17:16
1ኛ የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት
# ስለ ሰው ሕይወት መላላክ/ዕብ1:14
#እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ማመስገን።/ራእ4:8-11
#የሰውን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ማድረስ:ለሰው ልጅ ምሕረት መለመን/ዳን9:20:ሉቃ1:13:ዮሐ 10:3-5)
❤️የሰውን ነፍስ ወደ እግዚአብሔር ማቅረብ/መ.ሱቱ6:6-20
❤️ፍጥረተ ዓለምን:የሰውን ልጅ መጠበቅ/ማቴ18:10:ዳን4:13/
❤️ለምሕረተ ለመዓትም መላክ/ሮሜ9:22
❤️በመከራና በችግር ጊዜ ለተራዳኢነት መላክ/ዮሐ12:7-11/
❤️በፍጻሜ ዘመን ኃጥአንን ከጻድቃን መለየት/ማቴ24:31:ራዕ7:14
2ኛ ክብረ ቅዱሳን መላእክት
ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከበሩ እና ባለሟልነትንም ያገኙ ቅዱሳን በመሆናቸው በሰውም ዘንድ የተከበሩ ናቸው። ስለሆነም የአክብሮት ስግደት ይሰገድላቸዋል። በስማቸውም ቤተ ክርስቲያን እንድተነጽም ይደረጋል።
ዳን 8:15-18:ዘፍ22:31:ዘኁ22:31:ኢያ5:13
3ኛ ስለ ቅዱሳን ነብያት :ሐዋርያት :ሰማዕታት :ጻድቃን ክብር።
እነዚህ ቅዱሳን የየራሳቸው ተልዕኮ በገድል በትሩፋት የፈጸሙ ቅዱሳን ና ቅዱሳት በመሆናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ ልዩ ክብር አላቸው። የቃል ኪዳን ቅዱሳን በመሆናቸውም ምዕመናንን በስማቸው ወደ እግዚአብሔር ይማጸናሉ።
እነሱም በአጸደ ነፍስ ይማልዳሉ።ማቴ10:42:ዘጸ32:2-15:ሄኖክ12:33-40)
በነፍስ ሕያዋን ስለሆኑ/ሉቃ20:37-40/
በዚህም ምክንያት የአክብሮት ስግደት ይሰገድላቸዋል። እግዚአብሔር የሚወዳቸውና የሚያከብራቸው ስለሆኑ ራዕ3:9::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ።
Comments
Post a Comment