🌹ድርሳነ 🌹ቄርሎስ 🌹መግቢያ 🌹ክፍል ፩
ቅዱሳት መጻሕፍት እስትንፋሰ እግዚአብሔር እየተባሉ ይጠራሉ። ቅዱስ ቄርሎስ በኤፌሶን ጉባዔ ለ200ው ሊቃውንት አፈ ጉባዔ የነበረና ንስጥሮስን የረታ ታላቅ ሊቅ ነው። ይህ ቄርሎስ ትምህርት በጀመረ በአምስት ዓመቱ የብሉይ ኪዳንንና የሐዲስ ኪዳንን ትርጓሜ ተምሮ ያጠናቀቀ ቅዱስ ሊቅ ነው። ሲያስተምርም ከአንደበቱ ርቱዕነት ከጣዕመ ቃሉ ፍጹምነት ከትምህርተ ጥቅሱ ምሥጢርና ከምክሩ ከተግሣፁ የተነሣ የሚሰሙት ሁሉ ትምህርቱን አቋርጦ ይተውብን ይሆን ምነው ቢጨምርበት እያሉ ልቡናቸውን በተመሥጦ ሰቅለው ሕሊናቸውን አቅንተው ይሰሙት ነበር እንጂ አይሰለቹትም ነበር። ስመ ሥርጋዌው (የክብር ስሙ) መምህረ ዓለም ይባላል።
ቅዱስ ቄርሎስ ይህንን መጽሐፍ የጻፈው ከጉባዔ ኤፌሶን ጀምሮ ባለው ጊዜ ነው። ይህ መጽሐፍ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን ወልደ ማርያም ወልደ አብ መሆኑን ያስረዳል። ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ በሥጋ መሆኗን ይገልጻል። ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባሕርይ መሆኑን ያስረዳል። ይህ መጽሐፍ ውስጥ ለብዙ ከሓድያን ምላሽ ይሰጣል።
፩፦ የክርስቶስ ሥጋ ምትሐት ነው ለሚል ለማኒ
፪፦ ቃል ወደ ሥጋ ተለወጠ ለሚሉ ለሐራ ጥቃ
፫፦ የቃል መነሻ ከማርያም ወዲህ ነው ለሚሉ
፬፦ የቃል አካል አልነበረውም ለሚሉ
፭፦ ለሥጋ በነፍስ ምትክ መለኮት ሆነው ለሚሉ
፮፦ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ለሚሉ
እና ለመሳሰሉት ሁሉ ምላሽ የሚሰጥ ነው። የቃል መነሻ ከማርያም ወዲህ ነው የሚሉ እነ ፎጢኖስ ናቸው። ክርስቶስ ነፍስ የለውም በነፍሱ ምትክ መለኮቱ ሆነው የሚሉ እነ አቡሊናርዮስ ናቸው። ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ የሚል ንስጥሮስ ነው። ቃል ዝርው ነው አካል አልነበረውም የሚሉ እነ መርቅያን ናቸው።
ድርሳነ ቄርሎስን መማር ለሚፈልጉ ሼር አድርጉላቸው። ድርሳነ ቄርሎስ በደንብ ግልጽ እንዲሆንላችሁ በተከታታይነት የተማማርነውን ሃይማኖተ አበው በPDF ከዚህ ፖስት በፊት ያገኙታል።
© በትረማርያም አበባው
🌻ድርሳነ 🌻ቄርሎስ 🌻ክፍል ፪
ቄርሎስ ማለት አንበሳ ኃያል ኅሩይ (የተመረጠ፣ ምርጥ) ማለት ነው። አንበሳ መባሉ መ*ፍቃ*ንን እንደ አንበሳ በኃይለ ቃል ይሰብራቸዋልና ነው። የቅዱስ ቄርሎስን እናት ያሳደገቻት ኢትዮጵያዊት አገልጋይ ናት። ይህች ኢትዮጲያዊት መጀመሪያ ጣዖት አምላኪ ነበረች። በኋላ ቅዱስ አትናቴዎስን አጥምቀኝ ብላው ተጠምቃለች። ቴዎፍሎስ ሲሞት በእርሱ ምትክ ቅዱስ ቄርሎስ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኗል። ቅዱስ ቄርሎስ አፈጉባዔ ሆኖ የረታው መና*ቅ ንስጥሮስ ነው።
ንስጥሮስ የዲያድርስ የአጎቱ ልጅ ነው። ዲያድርስ የጳውሎስ ሳምሳጢ ደቀ መዝሙር ነው። ዲያድርስ ክሕደቱን ከጳውሎስ ሳምሳጢ ተማረ። ንስጥሮስ ደግሞ ክሕደቱን ከዲያድርስ ተማረ። ጳውሎስ ሳምሳጢ ግን ክሕደቱን ከዲያብሎስ ተምሮታል። ንስጥሮስ ከዲያድርስ የተማረውን ክሕደት ፕትርክና ሲሾም ገለጠው። አንዱን ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው አለ። ቅዱስ ቄርሎስ ይህንን በሰማ ጊዜ አከራክረኝ ብሎ ወደ ንጉሡ ቴዎዶስዮስ ላከበት።
ንጉሡም በኤፌሶን ጉባዔ እንዲሆን አዘዘ። 200 ሊቃውንት በአንድነት ሆነው ንስጥሮስን አውግዘው ለይተውታል። ቅዱስ ቄርሎስ በመዓርጉ ከሐዋርያት ከነቢያት የደረሰ ነበር። ንስጥሮስን ክሕደትን የካደች ምላስህ አትታዘዝህ ቢለው ምላሱ ተጎሎጉሎ ወጥቶ እንደውሻ ጓጉሮ ሞቷል። ቅዱሳን ምንም ባይከራከሩ ከጉባዔ አይለዩም። ቄርሎስ ምሥጢረ ተዋሕዶን በነበልባልና በሐመልማል፣ በእሳትና በብረት፣ በነፍስና በሥጋ ተዋሕዶ እየመሰለ ያስተምር ነበር።
© በትረማርያም አበባው
https://t.me/betremariyamabebaw/3862
🌷ድርሳነ 🌷ቄርሎስ 🌷ክፍል ፫
❤️ምዕራፍ ፩
በዚህ መጽሐፍ እስከ ምጽአት የሚነሱ ሊቃውንት መ*ና*ቃንን ሲረቱበት ይኖራሉ። ትክክለኛዋ ሃይማኖት ክርስቶስን አንድ አካል አንድ ባሕርይ የምትል ናት። ሰውን ጻድቅ ቢሉት ሐሰት፣ ንጹሕ ቢሉት ኃጢአት፣ ባዕል ቢሉት ንዴት ይስማማዋል። እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ዘአልቦ ሐሰት፣ ንጹሕ ዘአልቦ ኃጢአት፣ ባዕል ዘአልቦ ንዴት ነው።
❤️ምዕራፍ ፪
ናባል ዳዊት መጣ ቢሉት ደንግጦ እንደሞተ ሁሉ ነቢያት ክርስቶስ ይወርዳል ይወለዳል ብለው ሲያስተምሩ አጋንንት ይወጡ ነበረ። ዳዊት ኢዮአብን አቢሳን እየሰደደ ድል ያደርግ እንደነበረ ጌታም ነቢያትን እየሰደደ አጋንንትን ያስወጣ ነበረ።
❤️ምዕራፍ ፫
በአራቱ መዓዝን ምሉዕ ለሆነ ለእግዚአብሔር ምስጋና እንዲገባ ለቅዱሳንም የአክብሮት ስግደት መስገድ ይገባል። የሀብተ መንግሥት አስገኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በእውነተኛ ሃይማኖት ጸንተው ለሚወዱት ሰዎች ክህነትን መንግሥትን ፈጽሞ ይሰጣል።
❤️ምዕራፍ ፬
ነገሥታት አምልኮተ እግዚአብሔርን ቢይዙ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጣቸው የጸጋ ክብር አለ። ከእግዚአብሔር ትእዛዝ መውጣት አይገባም። አምላክ ሥነ ፍጥረትን የፈጠረ ለሰው ነው።
❤️ምዕራፍ ፭
ሰናክሬም በትዕቢት ሆኖ እግዚአብሔርን ተሳደበ። ንጉሡ ሕዝቅያስ ጌታ ሲሰደብ ሰምቶ ልብሱን ቀደደ አሰለበ። ልብስን መቅደድ የኀዘን ምልክት ነው። (እግዚአብሔር ሲሰደብ፣ ቤተክርስቲያን ስትሰደብ ማዘን ይገባል)።
❤️ምዕራፍ ፮
ሕዝቅያስ ጌታ ሲሰደብ በማዘኑ ጠላትን የማሸነፍ ሀብትን ከእግዚአብሔር ዘንድ አገኘ። ብዙ ሠራዊት የነበረው ሰናክሬምንም አሸነፈው። እግዚአብሔርን የማምለክ ፍሬው ይህ ነው። እኛ ምክንያት ሆነን እግዚአብሔርን ማሰደብ አይገባንም።
❤️ምዕራፍ ፯
ንጉሥ አኖሬዎስ ንጹሕ ድንግል ነው። ዐቢይ ጾምን ገዳመ አስቄጥስ እየሄደ ይጾም ነበር። ሐሰት የሌለባት አንድ አካል አንድ ባሕርይ የምትል ሃይማኖትን ለነፍሳችሁ ጌጥ አድርጓት። ሃይማኖት የልቡና መደገፊያ፣ የሰውነት ተድላ ደስታ፣ የራስ ዘውድ ናት።
© በትረ ማርያም አበባው
Comments
Post a Comment