Skip to main content

ነገረ ክርሰቶስ

 🌹ድርሳነ 🌹ቄርሎስ 🌹መግቢያ 🌹ክፍል ፩ 

ቅዱሳት መጻሕፍት እስትንፋሰ እግዚአብሔር እየተባሉ ይጠራሉ። ቅዱስ ቄርሎስ በኤፌሶን ጉባዔ ለ200ው ሊቃውንት አፈ ጉባዔ የነበረና ንስጥሮስን የረታ ታላቅ ሊቅ ነው። ይህ ቄርሎስ ትምህርት በጀመረ በአምስት ዓመቱ የብሉይ ኪዳንንና የሐዲስ ኪዳንን ትርጓሜ ተምሮ ያጠናቀቀ ቅዱስ ሊቅ ነው። ሲያስተምርም ከአንደበቱ ርቱዕነት ከጣዕመ ቃሉ ፍጹምነት ከትምህርተ ጥቅሱ ምሥጢርና ከምክሩ ከተግሣፁ የተነሣ የሚሰሙት ሁሉ ትምህርቱን አቋርጦ ይተውብን ይሆን ምነው ቢጨምርበት እያሉ ልቡናቸውን በተመሥጦ ሰቅለው ሕሊናቸውን አቅንተው ይሰሙት ነበር እንጂ አይሰለቹትም ነበር። ስመ ሥርጋዌው (የክብር ስሙ) መምህረ ዓለም ይባላል።


ቅዱስ ቄርሎስ ይህንን መጽሐፍ የጻፈው ከጉባዔ ኤፌሶን ጀምሮ ባለው ጊዜ ነው። ይህ መጽሐፍ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን ወልደ ማርያም ወልደ አብ መሆኑን ያስረዳል። ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ በሥጋ መሆኗን ይገልጻል። ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባሕርይ መሆኑን ያስረዳል። ይህ መጽሐፍ ውስጥ ለብዙ ከሓድያን ምላሽ ይሰጣል።

    ፩፦ የክርስቶስ ሥጋ ምትሐት ነው ለሚል ለማኒ

    ፪፦ ቃል ወደ ሥጋ ተለወጠ ለሚሉ ለሐራ ጥቃ

    ፫፦ የቃል መነሻ ከማርያም ወዲህ ነው ለሚሉ

    ፬፦ የቃል አካል አልነበረውም ለሚሉ 

    ፭፦ ለሥጋ በነፍስ ምትክ መለኮት ሆነው ለሚሉ

    ፮፦ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ለሚሉ

እና ለመሳሰሉት ሁሉ ምላሽ የሚሰጥ ነው። የቃል መነሻ ከማርያም ወዲህ ነው የሚሉ እነ ፎጢኖስ ናቸው። ክርስቶስ ነፍስ የለውም በነፍሱ ምትክ መለኮቱ ሆነው የሚሉ እነ አቡሊናርዮስ ናቸው። ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ የሚል ንስጥሮስ ነው። ቃል ዝርው ነው አካል አልነበረውም የሚሉ እነ መርቅያን ናቸው።


ድርሳነ ቄርሎስን መማር ለሚፈልጉ ሼር አድርጉላቸው። ድርሳነ ቄርሎስ በደንብ ግልጽ እንዲሆንላችሁ በተከታታይነት የተማማርነውን ሃይማኖተ አበው በPDF ከዚህ ፖስት በፊት ያገኙታል።


© በትረማርያም አበባው




🌻ድርሳነ 🌻ቄርሎስ 🌻ክፍል ፪


ቄርሎስ ማለት አንበሳ ኃያል ኅሩይ (የተመረጠ፣ ምርጥ) ማለት ነው። አንበሳ መባሉ መ*ፍቃ*ንን እንደ አንበሳ በኃይለ ቃል ይሰብራቸዋልና ነው። የቅዱስ ቄርሎስን እናት ያሳደገቻት ኢትዮጵያዊት አገልጋይ ናት። ይህች ኢትዮጲያዊት መጀመሪያ ጣዖት አምላኪ ነበረች። በኋላ ቅዱስ አትናቴዎስን አጥምቀኝ ብላው ተጠምቃለች። ቴዎፍሎስ ሲሞት በእርሱ ምትክ ቅዱስ ቄርሎስ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኗል። ቅዱስ ቄርሎስ አፈጉባዔ ሆኖ የረታው መና*ቅ ንስጥሮስ ነው።


ንስጥሮስ የዲያድርስ የአጎቱ ልጅ ነው። ዲያድርስ የጳውሎስ ሳምሳጢ ደቀ መዝሙር ነው። ዲያድርስ ክሕደቱን ከጳውሎስ ሳምሳጢ ተማረ። ንስጥሮስ ደግሞ ክሕደቱን ከዲያድርስ ተማረ። ጳውሎስ ሳምሳጢ ግን ክሕደቱን ከዲያብሎስ ተምሮታል። ንስጥሮስ ከዲያድርስ የተማረውን ክሕደት ፕትርክና ሲሾም ገለጠው። አንዱን ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው አለ። ቅዱስ ቄርሎስ ይህንን በሰማ ጊዜ አከራክረኝ ብሎ ወደ ንጉሡ ቴዎዶስዮስ ላከበት።


ንጉሡም በኤፌሶን ጉባዔ እንዲሆን አዘዘ። 200 ሊቃውንት በአንድነት ሆነው ንስጥሮስን አውግዘው ለይተውታል። ቅዱስ ቄርሎስ በመዓርጉ ከሐዋርያት ከነቢያት የደረሰ ነበር። ንስጥሮስን ክሕደትን የካደች ምላስህ አትታዘዝህ ቢለው ምላሱ ተጎሎጉሎ ወጥቶ እንደውሻ ጓጉሮ ሞቷል። ቅዱሳን ምንም ባይከራከሩ ከጉባዔ አይለዩም። ቄርሎስ ምሥጢረ ተዋሕዶን በነበልባልና በሐመልማል፣ በእሳትና በብረት፣ በነፍስና በሥጋ ተዋሕዶ እየመሰለ ያስተምር ነበር።


© በትረማርያም አበባው





https://t.me/betremariyamabebaw/3862





🌷ድርሳነ 🌷ቄርሎስ 🌷ክፍል ፫

                     ❤️ምዕራፍ ፩

በዚህ መጽሐፍ እስከ ምጽአት የሚነሱ ሊቃውንት መ*ና*ቃንን ሲረቱበት ይኖራሉ። ትክክለኛዋ ሃይማኖት ክርስቶስን አንድ አካል አንድ ባሕርይ የምትል ናት። ሰውን ጻድቅ ቢሉት ሐሰት፣ ንጹሕ ቢሉት ኃጢአት፣ ባዕል ቢሉት ንዴት ይስማማዋል። እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ዘአልቦ ሐሰት፣ ንጹሕ ዘአልቦ ኃጢአት፣ ባዕል ዘአልቦ ንዴት ነው።

                       ❤️ምዕራፍ ፪

ናባል ዳዊት መጣ ቢሉት ደንግጦ እንደሞተ ሁሉ ነቢያት ክርስቶስ ይወርዳል ይወለዳል ብለው ሲያስተምሩ አጋንንት ይወጡ ነበረ። ዳዊት ኢዮአብን አቢሳን እየሰደደ ድል ያደርግ እንደነበረ ጌታም ነቢያትን እየሰደደ አጋንንትን ያስወጣ ነበረ።

                       ❤️ምዕራፍ ፫

በአራቱ መዓዝን ምሉዕ ለሆነ ለእግዚአብሔር ምስጋና እንዲገባ ለቅዱሳንም የአክብሮት ስግደት መስገድ ይገባል። የሀብተ መንግሥት አስገኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በእውነተኛ ሃይማኖት ጸንተው ለሚወዱት ሰዎች ክህነትን መንግሥትን ፈጽሞ ይሰጣል።

                       ❤️ምዕራፍ ፬

ነገሥታት አምልኮተ እግዚአብሔርን ቢይዙ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጣቸው የጸጋ ክብር አለ። ከእግዚአብሔር ትእዛዝ መውጣት አይገባም። አምላክ ሥነ ፍጥረትን የፈጠረ ለሰው ነው።

                      ❤️ምዕራፍ ፭

ሰናክሬም በትዕቢት ሆኖ እግዚአብሔርን ተሳደበ። ንጉሡ ሕዝቅያስ ጌታ ሲሰደብ ሰምቶ ልብሱን ቀደደ አሰለበ። ልብስን መቅደድ የኀዘን ምልክት ነው።  (እግዚአብሔር ሲሰደብ፣ ቤተክርስቲያን ስትሰደብ ማዘን ይገባል)።

                      ❤️ምዕራፍ ፮

ሕዝቅያስ ጌታ ሲሰደብ በማዘኑ ጠላትን የማሸነፍ ሀብትን ከእግዚአብሔር ዘንድ አገኘ። ብዙ ሠራዊት የነበረው ሰናክሬምንም አሸነፈው። እግዚአብሔርን የማምለክ ፍሬው ይህ ነው። እኛ ምክንያት ሆነን እግዚአብሔርን ማሰደብ አይገባንም።

                      ❤️ምዕራፍ ፯

ንጉሥ አኖሬዎስ ንጹሕ ድንግል ነው። ዐቢይ ጾምን ገዳመ አስቄጥስ እየሄደ ይጾም ነበር። ሐሰት የሌለባት አንድ አካል አንድ ባሕርይ የምትል ሃይማኖትን ለነፍሳችሁ ጌጥ አድርጓት። ሃይማኖት የልቡና መደገፊያ፣ የሰውነት ተድላ ደስታ፣ የራስ ዘውድ ናት።


© በትረ ማርያም አበባው










Comments

Popular posts from this blog

የዕለቱ ወንጌል ሐምሌ 5

  05/11/2016 /ጴጥሮስ ወጳውሎስ ብርሃናተ ዓለም 72 አርድእት ወይስሐቅ ሰማእት/                       የዕለቱ የወንጌል ክፍል                          ዮሐንስ 21:15-20      ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን?” አለው። “አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው።“ግልገሎቼን አሰማራ፡” አለው። ደግሞ ሁለተኛ፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው። “አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ፡” አለው። “ጠቦቶቼን ጠብቅ፡” አለው። ሦስተኛ ጊዜ፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው። ሦስተኛ፦ “ትወደኛለህን?” ስላለው ጴጥሮስ አዘነና፦ “ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ፡” አለው። ኢየሱስም አለው፦ “በጎቼን አሰማራ። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል።” በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ፦ “ተከተለኝ፡” አለው።        ...

ወንጌል ዘሐምሌ 6

 ዕርገቱ ለዕዝራ ነቢይ ወንስተሮኒን ወአልሞድያስ ወሥርቀተ ተሙዝ ወዮልዮህ ወተዝካረ በርተሎሜዎስ ወ፲፻ ሰማዕታት ወከላድያን ሊቀ ጳጳሳት                      06/11/2016                    የዕለቱ የወንጌል ክፍል     “እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉት ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በሰገነትም ያለ በቤቱ ያለውን ሊወስድ አይውረድ፥ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያችም ወራት ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤ “በዚያን ጊዜ ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ እንግዲህም ከቶ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናልና። እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ። በዚያን ጊዜ ማንም፦ እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፡ ወይም፦ ከዚያ አለ፡ ቢላችሁ አትመኑ፤ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ። እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ። እንግዲህ፦ ‘እነሆ፥ በበረሀ ነው’ ቢሉአችሁ፥ አትውጡ፤ ‘እነሆ፥ በእልፍኝ ነው’ ቢሉአችሁ፥ አትመኑ፤ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥...

የዕለቱ ወንጌል ሐምሌ 7:

 አባ ሲኖዳ ወአግናጥዮስ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጊዮርጊስ ወመቃቢስ ወአግራጥስ ወቦኡ ሥሉስ ቅዱስ ቤተ አብርሃም የዕለቱ ወንጌል ሐምሌ 7: ዮሐ  8:51-59 ፶፩እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።፶፪አይሁድ። ጋኔን እንዳለብህ አሁን አወቅን። አብርሃም ስንኳ ሞተ ነቢያትም፤ አንተም። ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አይቀምስም ትላለህ።፶፫በእውኑ አንተ ከሞተው ከአባታችን ከአብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማንን ታደርጋለህ? አሉት።፶፬ኢየሱስም መለሰ አለም። እኔ ራሴን ባከብር ክብሬ ከንቱ ነው፤ የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው፤፶፭አላወቃችሁትምም፥ እኔ ግን አውቀዋለሁ። አላውቀውም ብል እንደ እናንተ ሐሰተኛ በሆንሁ፤ ዳሩ ግን አውቀዋለሁ ቃሉንም እጠብቃለሁ።፶፮አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው።፶፯አይሁድም። ገና አምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት።፶፰ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው።፶፱ስለዚህ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ተሰወራቸው ከመቅደስም ወጥቶ በመካከላቸው አልፎ ሄደ ።"" ሮሜ9:1-17 ፩-፪ብዙ ኀዘን የማያቋርጥም ጭንቀት በልቤ አለብኝ ስል በክርስቶስ ሆኜ እውነትን እናገራለሁ፤ አልዋሽምም፤ ሕሊናዬም በመንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል።፫በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና ..."" 1ኛዮሐ 4:11-21 የሐዋ 11:11-19 ምስባክ መዝ 27:8-9 ወሐሠሥኩ ገጽከ ገጸ ዚአከ አሐሥሥ እግዚኦ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ ፰አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ። አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።፱ፊትህ...